የተከበሩ አፈ ጉባኤ መልእክት

አራተኛው የፌዴሬሽን ም/ቤተ መስከረም 24/2003 ዓ. ከተመሠረተ ወዲህ ባለፉት ወራት ውስጥ ህገ መንግሰታዊ ተልዕኮውን በመወጣት በዕቅድ ከተያዙት ተግባራት ውስጥ በተጨማሪ የተለያዩ ሥራዎችን አከናውኗል በማከናወን ላይ ነው፡፡
ምክር ቤታችን በህገ መንገሰታዊ ተቋማት ተልዕኮውን ለመወጣት በመንግስት ከተየዘውና ሰፊ መሠት ያለው ፈጣን፣ ቀጣይና ፈትሀዊ የኤኮኖማ ዕድገትና ልማት የማፋጠንና ድህነትን የማስወገድ ዓላማ ያደረገውን የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድን ተግባራዋ በማድረግ የአገራችንን በሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች የሚኖራቸውን ሚና በማጎልበት በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡
የአገራችን በሌሮች፣ ብሔረሰባችና ህዝቦች በአገራችን ሲከናወኑ የቆዩት የልማት የዲሞክራሲ ሰርዓት ግንባታ ተግባራት ተሳታፊና ተቃሚዎች መሆናቸውን ይታወቃል ፡፡ ዛሬም የተጀመረውን የእድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ተግባራዋ ለማድረግ እጅ ለእጅ ተያይዘው በመረባረብ ላይ ይገኛሉ፡፡ በዚህም ዕቅዱን ከየአካባቡው ሁኔታ ጋር በማጣጣመና በመዘርዘር የላቀ ጠቅም በሚያስገኝላቸው አተገባበረ በመከወነ የተጀመረውን የአገራዊ ህዳሴ ጉዞ ማስቀጠል እንዲችሉ ምክር ቤታችን የራሱን ሚና በመጫወት ላይ ይገኛል፡፡
ካሣ ተክለብርሃን
የፌዴሬሽነ ምክር ቤተ አፈጉባኤ