|
Nation nationality song prepared by House of Federation of FDRE
More Video | ለህዳር 29 ለመወያያ የቀረበ ሰነዶች ህዳር 29 የብሔሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በዓል አከባበር በስኬት በመጠናቀቁ ሂደት የህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች ሚና ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው የተገለፀው ጥቅምት 14 ቀን 2005 ዓ.ም. በጊዮን ሆቴል ለ7ኛ ጊዜ የሚከበረውን የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል አከባበርና ቅድመ ዝግጅቱን አስመልክቶ ለባለሙያዎቹ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ነው፡፡ ውይይቱን በንግግር የከፈቱት አቶ ሙርሳን ኡመር በመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት የበዓሉ ንዑስ አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ ናቸው፡፡ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በ3ኛው የፓርላማ ዘመን 1ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ በ2ኛ መደበኛ ጉባኤው ሚያዚያ 21 ቀን 1998 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች የቃል ኪዳን ሰነዳቸው የሆነው የፌዴራል ህገ መንግሥት የፀደቀበት ህዳር 29 የህገ መንግሥት ቀን /የብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል/ እንዲሆን በወሰነው መሠረት ከ1999 ጀምሮ በተለያዩ ክልሎች በተለያዩ ዝግጅቶች በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን፤ ዘንድሮም ለ7ኛ ጊዜ “ብዙም አንድም ሆነን በመለስ ራዕይ፤ በህገ መንግሥታችን ለህዳሴያች” በሚል መሪ ቃል በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በባህርዳር ከተማ በደማቅ ሁኔታ እንደሚከበርና ቅድመ ዝግጅቱም እየተጠናቀቀ መሆኑም ተብራርቷል፡፡ በዓሉ በአገራችን በሁሉም ክልሎች ዞኖች ወረዳዎችና ከተሞች እንዲሁም በመንግሥታዊ ተቋሞች በትምህርት ቤቶች እና ዩኒቨርስቲዎች በድምቀት እንደሚከበር ተገልጿል፡፡ የበዓሉ አንድምታም /ፋይዳው/ በብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች መካከል መቀራረብ በመፍጠርና በማስተዋወቅ ብሔራዊ መግባባትን በማጠናከር በመፈቃቀድና በመቻቻል ላይ የተመሠረተ አንድነት ስር እንዲሰድ አንድ ኢኮኖሚና ፖለቲካ ማህበረሰብ በመገንባት ዜጐች በጋራ ልማቱ እንዲሳተፉ በማድረግ ጠላታችን በሆነው ድህነት ላይ የጋራ ክንዳቸውን እንዲያነሱ ማበረታታት ሲሆን፤ በተለይም ባለራዕዩ ታላቁ መሪያችን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ አገራችንን ጠላታችን ከሆነው ድህነት ለማላቀቅና የህዳሴ ጉዟአችንን በማሳካት የህዝቦችን የጋራ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የነደፉትን ራዕይ በቁጭት ለማስቀጠል ቃላቸውን የሚያድሱበት እንደሆነም ተብራርቷል፡፡ በመሆኑም ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በሕገ መንግሥቱና በፌዴራል ሥርዓቱ የተጐናፀፉትን ድሎች በመንከባከብ የአብሮነት ትሩፋቶችን በመጠበቅና በማጣጣም ከድህነት በላይ ጠላት አለመኖሩን ተገንዝበው የሞት ሽረት ትግላችን ቀጣይነት እንዲኖረው ቃላቸውን እንዲያድሱ በዓሉ ወሳኝ ድርሻ እንዳለው ተሰምሯል፡፡ በዚህ ሂደት በየደረጃ ያሉ የህዝብ ግንኙነት እና የሚዲያ ባለሙያዎች ሚና የጐላ ሲሆን፤ ለዜጐች በቂ ሽፋን በመስጠት የበኩላቸውን ድርሻ በንቃት መወጣት እንዳለባቸው የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት አስገንዝቧል፡፡ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በዓሉን አስመልክቶ በተለያዩ አካባቢዎችና ተቋማት የሚካሄዱትን መድረኮችንና ሲምፖዚየሞችን እንዲሁም በዓሉን በማስተዋወቅና ገጽታን በመገንባት ሂደት የበኩላቸውን የዜግነት ኃላፊነታቸውንና ግዴታቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል፡፡ በውይይት መድረኩ ከፌዴራል የመንግሥት ተቋማትና ከክልሎች የተጋበዙ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡
| |